የሃማስ ፖሊት ቢሮ ሃላፊ ቴህራን ውስጥ መገደሉን ተከትሎ በኢራን የሶስት ቀናት ሀዘን ታውጇል

ሰብስክራይብ
  የሃማስ ፖሊት ቢሮ ሃላፊ ቴህራን ውስጥ መገደሉን ተከትሎ በኢራን የሶስት ቀናት ሀዘን ታውጇልየሃማስ የፖሊት ቢሮ ሃላፊ ኢስማኢል ሃኒዬ የስንብት ስነ ስርዓት እ.ኤ.አ ነሐሴ 1 በቴህራን እንደሚካሄድ የኢራን የዜና ወኪል ፋርስ በዛሬው ዕለት ዘግቧል።በትላንትናው እለት የፍልስጤም ንቅናቄ ሃማስ ሃኒዬህ በኢራን ዋና ከተማ ቴህራን በሚገኘው መኖሪያ ቤቱ ላይ እስራኤል በፈጸመችው የአየር ጥቃት ምክንያት መሞቱን አረጋግጧል።በሃማስ መረጃ መሰረት ሃኒዬ የአዲሱ የኢራን ፕሬዝዳንት የሹመት ስነ ስርዓት ላይ ከተሳተፈ በኋላ ቴህራን በሚገኘው መኖሪያ ቤቱ ላይ እስራኤል በፈጸመቸው “ ጥቃት” ተገድሏል ብሏል።ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0