የሐምሌ 24 ምሽት ዋና ዋና የዓለም ዜናዎች

ሰብስክራይብ
የሐምሌ 24 ምሽት ዋና ዋና የዓለም ዜናዎች🟠 ፑቲን ከተመራጩ የኢንዶኔዢያ ፕሬዝዳንት ፕራቦዎ ሱቢያንቶ ጋር ተገናኝተዋል፤ ሀገራቱ ለረጅም ጊዜ የዘለቀ ወዳጅነት እንዳላቸውም ጠቁመዋል። እንደ ሩሲያ ፕሬዝዳንት ገለጻ የንግድ ግንኙነቶች በተሳካ ሁኔታ እያደገ በመሄዱ፤ በቅርብ ዓመታት ውስጥ የንግድ ልውውጥ በእጥፍ እንደጨመረም ተናግረዋል።🟠 ቴህራን የሐማስ ፖሊት ቢሮ ሃላፊ  መገደሉን ተከትሎ በልዩ እርምጃ ምላሽ እንደምትሰጥ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኢራን ተወካይ አስታውቀዋል።🟠 የእስራኤል የመከላከያ ሚኒስትር ሀገሪቱ ጦርነትን እንደማትፈልግ ገልጸው ነገር ግን ሊኖር ለሚችል ማንኛውም ሁነት ምላሽ ለመስጠት ዝግጁ መሆኗን ተናግረዋል።🟠 የጀርመን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እ.አ .አ በ2021 በሀገሪቱ የካርታ ስራ ኤጀንሲ ላይ ደርሶ በነበረው የሳይበር ጥቃት የቻይናን አምባሳደር አስጠርቶ እንደነበር ተነግሯል።🟠  የጆርጂያ መንግስት እየወሰደ ያለው እርምጃ የአውሮፓ ህብረት እና የኔቶ አባል ለመሆን ከሚጠበቅበት ተግባር ጋር የማይጣጣም ነው በማለት አሜሪካ ለጆርጂያ የምትሰጠውን እርዳታ ለጊዜው ማቆሟን የዩኤስ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ብሊንከን ተናግረዋል።ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0