የሩሲያ ኩባንያዎች በደቡብ አፍሪካ የመከላከያ ኤክስፖ ላይ እንደሚሳተፉ የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል

ሰብስክራይብ
የሩሲያ ኩባንያዎች በደቡብ አፍሪካ የመከላከያ ኤክስፖ ላይ እንደሚሳተፉ የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋልበመስከረም ወር በደቡብ አፍሪካ በሚጀመረው "አፍሪካ ኤሮስፔስ ኤንድ ዲፌንስ 2024" በተሰኘው በአፍሪካ ትልቁ የመከላከያ እና አቪዬሽን ኤግዚቢሽን የመንግስት ንብረት የሆኑት ሮሶቦሮን ኤክስፖርት እና ሮስኮስሞስን ጨምሮ ቢያንስ 6 የሩሲያ ኩባንያዎች እንደሚሳተፉ የደቡብ አፍሪካ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።በሀገሪቱ ዋና ከተማ ፕሪቶሪያ አቅራቢያ በሚገኘው ዋተርክሎፍ አየር ሃይል ጣቢያ በሚካሄደው ዝግጅት ላይ የኩባንያዎቹ ተሳትፎ የተረጋገጠ ሲሆን የቅርብ ጊዜ ምርቶቻቸውን የሚያሳዩበት መድረክ እንደሚሆን ተነገሯል።በተጨማሪም ሩሲያ በኤግዚቢሽኑ ላይ ሱፐርሶኒክ ቱ-160 ስትራቴጅካዊ ቦምብ ጣይ ተዋጊ አውሮፕላኗን ልታሳይ ትችላለች የተባለ ሲሆን፤ እንደ ዘገባው ከሆነ ሰባት የሩስያ ጦር ስፔሻሊስቶች ቡድን ለቦምብ ጣዩ ቱ-160 መምጣት ዝግጅት ለማድረግ በዚህ ሳምንት ዋተርክሎፍን መጎብኘታቸው ተገልጿል።ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0