የካሊፎርኒያ ትልቁ የሰደድ እሳት በፍጥነት መባባሱን ቀጥሎ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ለስደት ዳረገ

ሰብስክራይብ
የካሊፎርኒያ ትልቁ የሰደድ እሳት በፍጥነት መባባሱን ቀጥሎ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ለስደት ዳረገ በዩናይትድ ስቴትስ ሰሜን ካሊፎርኒያ ግዛት ከተነሱት በርካታ የሰደድ እሳቶች አንዱ የሆነው የፓርክ ፋየር ቺኮ ከተማ ውስጥ ተቀስቅሶ ከሁለት ቀናት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ወደ ግዛቱ ግዙፍ የሰደድ እሳትነት ተቀይሯል። እሳቱ ህንፃዎችን እንዳወደመ እና በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን እንዳፈናቀለ የተነገረ ሲሆን እስካሁን ከ307,000 በላይ ሄክታር መሬት አንድዷል። በሰዓት ከ4,000 እስከ 5,000 ሄክታር በሚደርስ ፍጥነት እየነደደ ያለማቋረጥ እየተባባሰ መጥቷል። እሳቱን አስጀምሯል የተባለ አንድ ግለሰብ ተይዞ ክስ ተመስርቶበታል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0