የሐምሌ 18 ምሽት ዋና ዋና የዓለም ዜናዎች

ሰብስክራይብ
የሐምሌ 18 ምሽት ዋና ዋና የዓለም ዜናዎች 🟠 የሩሲያ እና ቤላሩስ ፕሬዝዳንቶች በቫላም ደሴት ተገናኝተው በእምላክ እናት አምሳያ የስሞልንስክ ቤተክርስቲያን የጸሎት ሥነ-ሥርዓት አካሂደዋል። 🟠 በኪዬቭ ይፋ የተደረገው የድርድር ዝግጁነት ከሞስኮ የዲፕሎማሲ መንገድ ተመራጭ ነው ከሚል አቋም ጋር የሚስማማ እንደሆነ በተመድ የሩሲያ ቋሚ ተወካይ ተናገሩ። ኪዬቭ ለሰላም እቅድ ዝግጁ ከሆነች በፑቲን የቀረበውን የሰላም ተነሳሽነት እንድትመለከትና ዩክሬን ከዚህ የተሻለ አማራጭ እንደማታገኝ ተናግረዋል። 🟠 የዩክሬን ባህር ሃይል ነው ተብሎ የተገመተ ፈንጂ የያዘ ጄት ስኪ በኢስታንቡል የባህር ዳርቻ መገኘቱን አይ.ኤች.ኤ የዜና ወኪል ዘግቧል። 🟠 ካማላ ሃሪስ ለአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ፉክክር የሚያደርጉትን ዘመቻ የመጀመሪያ ቪዲዮ በመልቀቅ ጀምረዋል። 🟠 1.4 ሚሊየን ሊትር የነዳጅ ዘይት የጫነ ታንኳ በማኒላ ቤይ ረቡዕ እለት ሰጠመች። የነዳጅ ምርቶች ከአደጋው በኋላ ብዙም ሳይቆይ መፍሰስ የጀመሩ ሲሆን የፊሊፒንስ ባለስልጣናት ፍሳሹን ለመጠገን እና የነዳጅ ምርቶችን በአንድ ሳምንት ውስጥ ለማውጣት እቅድ እንዳላቸው ተናግረዋል። 🟠 በፊሊፒንስ በካሪና አውሎ ነፋስ በደረሰ የጎርፍ አደጋ 14 ሰዎች መሞታቸውን የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። አደጋው ከ900,000 በላይ ሰዎችን ያጠቃ ሲሆን በደርዘን የሚቆጠሩ በረራዎች ተሰርዘዋል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0