የሐምሌ 16 ቀትር ዋና ዋና የዓለም ዜናዎች

ሰብስክራይብ
የሐምሌ 16 ቀትር ዋና ዋና የዓለም ዜናዎች🟠  በማሪዮፖል ዲፒአር በቤልጎሮድ ክልል የሚገኘውን መስጊድ ለማቃጠል  በዩክሬን ደህንነት አገልግሎትየተሰጣቸውን ትዕዛዝ ሊፈፅሙ የነበሩ ሁለት የሩሲያ ዜጎችን መያዙን የሩሲያ የፌደራል ደህንነት አገልግሎት አስታወቀ።🟠 የዩክሬን ሰው አልባ አውሮፕላኖች በሩሲያ ካቭካዝ ወደብ በጀልባ ላይ ባደረሱት ጥቃት አንድ ሰው ሲሞት አምስት ደግሞ መቁሰላቸውን የኩባን ኦፕሬሽን አገልግሎት አስታወቀ።🟠 የሩሲያ አየር መከላከያ ሰራዊት 25 የዩክሬን ሰው አልባ አውሮፕላኖችን፤ ከዚህም ውስጥ 21 ያህሉ በክራይሚያ እና በጥቁር ባህር ላይ ተመትተው መውደቃቸውን የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ።🟠 የባይደን ከምርጫ ውድድሩ እራሱን ማግለሉ በውጭ ፖሊሲ ዙሪያ እንደፈለገ በነጻነት እንዲንቀሳቀስ ያስችለዋል ሲል ፋይናንሺያል ታይምስ ዘግቧል።🟠 ካማላ ሃሪስ የዲሞክራቲክ ፕሬዝዳንታዊ እጩ ሆነው ለመቅረብ የሚያስችላቸውን በቂ የውክልና ድምፅ እያገኙ መሆኑን አሶሼትድ ፕሬስ ዘግቧል።ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0