ሁቲዎች በእስራኤል እና በቀይ ባህር ላይ በምትገኝ የአሜሪካ መርከብ ላይ ጥቃት መሰንዘራቸውን ገለፁ

ሰብስክራይብ
ሁቲዎች በእስራኤል እና በቀይ ባህር ላይ በምትገኝ የአሜሪካ መርከብ ላይ ጥቃት መሰንዘራቸውን ገለፁ "የየመን ጦር ሃይሎች የሚሳኤል ሃይል በደቡባዊ ኡሙ አል-ራሽሽ አካባቢ እስራኤል የፍልስጤምን ግዛት በሃይል በተቆጣጠረችባቸው አካባቢዎች ላይ በበርካታ ባላስቲክ ሚሳኤሎች ወሳኝ የሆኑ ኢላማዎችን በመምታት ልዩ ወታደራዊ ዘመቻ ፈፅሟል። የሃውቲ ጦር ቃል አቀባይ ያህያ ሳሬ የሃውቲ የባህር፣ የድሮን እና የሚሳኤል ጦር፤ በቀይ ባህር ላይ የነበራቸውን     'ፑምባ ' የተባለችውን የአሜሪካ መርከብ በበርካታ ባለስቲክ ሚሳኤሎች እና ሰው አልባ አውሮፕላኖች ጥቃት መፈጸማቸውን ተናግሯል። በመርከቧ ላይ ቀጥተኛ የሆነ ጥቃት መፈፀሙን አክሎ ገልጿል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0