የኬንያ ፕሬዝዳንት 11 ሚኒስትሮችን በመሾም አዲስ መንግስት የማዋቀር ሂደት ጀመሩ

ሰብስክራይብ
የኬንያ ፕሬዝዳንት 11 ሚኒስትሮችን በመሾም አዲስ መንግስት የማዋቀር ሂደት ጀመሩ ዊሊያም ሩቶ "የሀገሪቱን አስቸኳይ እና የማይቀለበስ ለውጥ የሚደግፍ አዲስ ሰፊ ካቢኔ የማዋቀር ሂደት ጀምሬያለሁ" ብለዋል በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ። ስድስቱ ሚኒስትሮች ሐምሌ 4 በተበተነው የቀድሞው መንግስት አባል ነበሩ። ሆኖም ሚኒስትሮቹ አሁንም የፓርላማ ይሁንታ ያስፈልጋቸዋል። የኬንያ መንግሥት ለሳምንታት የዘለቀውን ተቃውሞ ለማስቆም ጥረቱን አጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን ወንጀለኛ ቡድኖች ተቃውሞ ሰልፉን ጠልፈዋል ያለው ፖሊስ በማእከላዊ ናይሮቢ ሰልፍ ለማገድ ሞክሯል። ይሁን እንጂ በናይሮቢ የሚገኘው ከፍተኛ ፍርድ ቤት የህዝብ ጥቅም ቡድኑ ካቲባ ኢንስቲትዩት ያቀረበው ክስ ታይቶ ውሳኔ እስኪሰጥ ድረስ የፖሊስ እገዳውን ለግዜው እንዳነሳ ተዘግቧል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0