የሐምሌ 12 የምሽት ዋና ዋና የዓለም ዜናዎች፡-

ሰብስክራይብ
የሐምሌ 12 የምሽት ዋና ዋና የዓለም ዜናዎች፡- 🟠 የኬንያ ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ አዲስ መንግሥት የማቋቋም ሂደት ጀምረው 11 ሚኒስትሮችን ሾመዋል። 🟠 የዓለም አቀፉ የፍትህ ፍርድ ቤት እስራኤል በፍልስጤም ግዛቶች ውስጥ ያላትን ህገ-ወጥ ይዞታ በፍጥነት እንድታቆም እና ለደረሰ ጉዳት ካሳ እንድትከፍል ወስኗል። ኔታንያሁ የፍርድ ቤቱን ውሳኔ ውድቅ አድርገዋል። 🟠 በዓለም ዙሪያ ከ2,200 በላይ በረራዎች የተሰረዙ ሲሆን ወደ 24,000 የሚጠጉ በረራዎች በዓለም አቀፍ ደረጃ በተፈጠረው መስተጓጎል እንደዘገዩ ፍላይትዌር ዘግቧል። ባይደን ማይክሮሶፍት በዓለም አቀፍ  ደረጃ መቋረጡን በተመለከተ ገለፃ እንደተደረገላቸው እና ባለስልጣኖቻቸው ከተጠቁ ኩባንያዎች ጋር ግንኙነት እያደረጉ መሆኑን ዋይት ሀውስ ገልጿል። የሩሲያ አየር መንገዶች ከረጅም ጊዜ በፊት ወደ የሀገር ውስጥ የቦታ ማስያዣ ስርዓት በመቀየረቻው በዓለም አቀፉ መስተጓጎል አልተጎዱም። 🟠 በሊድስ እንግሊዝ የተቀሰቀሰው የሌሊት ሁከት ሮማንያውያን ልጆች ከቤተሰቦቻቸው በመወሰዳቸው ምክንያት የተነሳ እንደሆነ የሮማንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። 🟠 የቬትናም ኮሚኒስት ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ ዋና ፀሀፊ ንጉየን ፉ ትሮንግ በ81 ዓመታቸው አርብ ዕለት ከዚህ አለም በሞት ተለዩ። 🟠 የዩክሬን አትሌቶች በፓሪስ ኦሎምፒክ ለሩሲያውያን ሰላምታ እንዳይሰጡ ተፈቅዶላቸዋል ሲሉ የዩክሬን ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዝዳንት ተናግረዋል። በኦሎምፒኩ 15 ሩሲያውያን ብቻ የሚሳተፉ ሲሆን እነሱም በገለልተኝነት ይወዳደራሉ። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0