ትራምፕ ቀጣዩ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ሆነው ከተመረጡ ከሰሜን ኮሪያ መሪ ጋር እንደሚስማሙና ኪም እናፍቀዋለሁ ሲሉ ተናገሩ

ሰብስክራይብ
ትራምፕ ቀጣዩ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ሆነው ከተመረጡ ከሰሜን ኮሪያ መሪ ጋር እንደሚስማሙና ኪም እናፍቀዋለሁ ሲሉ ተናገሩ "ከሰሜን ኮሪያና ኪም ጆንግ ኡን ጋር በጣም ተግባብተን ነበር…ብዙ የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ካለው  ሰው ጋር መስማማት ጥሩ ነው፤ አለበለዚያ" ብለዋል ትራምፕ። "ከሱ ጋር መግባባት በመቻላችን ከሰሜን ኮሪያ የሚወነጨፉ ሚሳኤሎችን ማስቆም ችለናል። አሁን ሰሜን ኮሪያ እንደገና እያስቸገረች ነው፣ ነገር ግን ስንመለስ [ወደ ኋይት ሀውስ] ከእሱ ጋር እስማማለሁ፣ እኔንም ተመልሶ ሊያየኝ ይፈልጋል። እውነቱን ማወቅ ከፈለጋችሁ ሳልናፍቀው አልቀርም ብዬ አስባለሁ።" እ.አ.አ. በ2018 ትራምፕ እና የሰሜን ኮሪያው መሪ በዩናይትድ ስቴትስ እና ሰሜን ኮሪያ መካከል ያለውን ውጥረት ለማርገብ የጋራ ስምምነት ተፈራርመው ነበር። ሁለቱ መሪዎች በተከታዩ ዓመት በቬትናም ሃኖይ ድርድሩን ለመቀጠል ቢገናኙም አሜሪካ በሰሜን ኮሪያ ላይ በጣለችው ማዕቀብ ምክንያት ስምምነት ላይ መድረስ አልቻሉም። ከዛ ጊዜ ጀምሮ የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ውጥረት ውስጥ ይገኛል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0