የሐምሌ 12 ረፋድ ዋና ዋና የዓለም ዜናዎች፡-
🟠 ከሩሲያ ጋር ያላት ትብብር ለቶጎ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ እንዳለው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሮበርት ዱሴይ ለስፑትኒክ ተናግረዋል።
🟠 ፕሬዝዳንት ራማፎሳ በድጋሚ ከተመረጡ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ለህዝብ ባደረጉት ንግግር የሀገሪቱ የማምረት አቅም ለበርካታ ዓመታት ሲያሽቆለቁል በመቆየቱ መንግሥታቸው ደቡብ አፍሪካን በድጋሚ ኢንዱስትራላይዝ በማድረግ የስራ እድል ለመፍጠር እንዳሰበ ገልፀዋል፡፡
🟠 በናይጄሪያ ዝቅተኛው የወር ደመወዝ ወደ 70,000 ናይራ (44 ዶላር) ከፍ ማለቱን የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት አማካሪ አስታውቀዋል።
🟠 የኬንያ መንግስት የተቃውሞ ሰልፎች እንዲቆሙ በድጋሚ የጠየቀ ሲሆን ፖሊስ በማእከላዊ ናይሮቢ የሚደረጉ ሰልፎችን ለማገድ ሞክሯል፡፡
🟠 የሩዋንዳ ፕሬዝዳንት ፖል ካጋሜ 99.18% ድምጽ በማግኘት ለአራተኛ ጊዜ በድጋሚ መመረጣቸውን ብሔራዊ ምርጫ ኮሚሽን ገልጿል፡፡
🟠 ቤልጎሮድ ክልል ሼቤኪኖ ከተማ የኪዬቭ ጦር ባደረሰው ጥቃት አንድ ሰው እንደቆሰለና ሰባት የግል ቤቶች ላይ ጉዳት መድረሱን አስተዳዳሪው አስታውቀዋል።
🟠 የዩክሬን ሃይል ሉሃንስክ ውስጥ ሶስት የአሜሪካ አታካም ሚሳኤሎችን እንደተኮሰ ተዘግቧል።
🟠 ትራምፕ በህዳር ወር በሚካሄደው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ሪፐብሊካን ፓርቲን ወክለው ለመወዳደር መስማማታቸውን ገልጸዋል።
🟠 ባይደን ካማላ ሃሪስ በፕሬዝዳንታዊ ፉክክሩ የሚተኳቸው ከሆነ ምርጫውን የማሸነፍ እድላቸውን በተመለከተ የአሜሪካውያንን አመለካከት ለማወቅ ጥናት እንዲደረግ ማዘዛቸውን መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
🟠 አርብ ጠዋት ዋና ዋና የአሜሪካ አየር መንገዶች ከፍተኛ የስራ እንቅስቃሴ መቆራረጥ ገጥሟቸው በረራዎችን ለግዜው እንደሰረዙ አስታውቀዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
https://amh.sputniknews.africa/20240719/5825.html
የሐምሌ 12 ረፋድ ዋና ዋና የዓለም ዜናዎች፡-
የሐምሌ 12 ረፋድ ዋና ዋና የዓለም ዜናዎች፡-
Sputnik አፍሪካ
የሐምሌ 12 ረፋድ ዋና ዋና የዓለም ዜናዎች፡- 🟠 ከሩሲያ ጋር ያላት ትብብር ለቶጎ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ እንዳለው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሮበርት ዱሴይ ለስፑትኒክ ተናግረዋል። 🟠 ፕሬዝዳንት ራማፎሳ በድጋሚ ከተመረጡ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ለህዝብ ባደረጉት... 19.07.2024, Sputnik አፍሪካ
2024-07-19T12:39+0300
2024-07-19T12:39+0300
2024-07-19T13:20+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2024
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий