ቤላሩስ የትራክተሮችን ኤክስፖርት ወደ አፍሪካ ለማዞር አስባለች

ሰብስክራይብ
ቤላሩስ የትራክተሮችን ኤክስፖርት ወደ አፍሪካ ለማዞር አስባለች የቤላሩስ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ፒዮትር ፓርክሆምቺክ "የአፍሪካ ሀገራት ገበያዎች ተስፋ ሰጪ እንደሆኑ ተለይተዋል። ድርድሮች እየተካሄዱ ነው፤ ሁሉም ነገር በውጤቱ ላይ የተመሰረተ ነው" ብለዋል። የቤላሩስ ባለስልጣናት አሁን "የኤክስፖርት ፍሰቶችን ለማዞር አዳዲስ ገበያዎችን በንቃት እየፈለጉ ነው።" ከሰኔ 24 ጀምሮ የቤላሩስ ትራክተሮች ወደ አውሮፓ ህብረት እንዲገቡ አይፈቀድላቸውም። እንደ አውሮፓ ህብረት ምክር ቤት ገለጻ እነዚህ ገዳቢ እርምጃዎች ሩሲያ የአውሮፓ ማዕቀቦችን ለማምለጥ የምታደርገውን ጥረት ለመዋጋት እና "የሩሲያ እና የቤላሩስ ኢኮኖሚን ከፍተኛ ውህደት" ግምት ውስጥ የከተተ ነው። ፒዮትር ፓርክሆምቺክ "ወቅቱ በጣም አስቸጋሪ ነው" ነገር ግን የቤላሩስ ባለስልጣናት "ችግሮቹን እየተቋቋሙ ነው" ብለዋል። እንደ እርሳቸው ገለጻ "ተግዳሮቶቹ በበቂ ሁኔታ ተገምግመው ምላሽ ያገኛሉ።" ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0