ቤላሩስ የትራክተሮችን ኤክስፖርት ወደ አፍሪካ ለማዞር አስባለች
የቤላሩስ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ፒዮትር ፓርክሆምቺክ "የአፍሪካ ሀገራት ገበያዎች ተስፋ ሰጪ እንደሆኑ ተለይተዋል። ድርድሮች እየተካሄዱ ነው፤ ሁሉም ነገር በውጤቱ ላይ የተመሰረተ ነው" ብለዋል።
የቤላሩስ ባለስልጣናት አሁን "የኤክስፖርት ፍሰቶችን ለማዞር አዳዲስ ገበያዎችን በንቃት እየፈለጉ ነው።"
ከሰኔ 24 ጀምሮ የቤላሩስ ትራክተሮች ወደ አውሮፓ ህብረት እንዲገቡ አይፈቀድላቸውም። እንደ አውሮፓ ህብረት ምክር ቤት ገለጻ እነዚህ ገዳቢ እርምጃዎች ሩሲያ የአውሮፓ ማዕቀቦችን ለማምለጥ የምታደርገውን ጥረት ለመዋጋት እና "የሩሲያ እና የቤላሩስ ኢኮኖሚን ከፍተኛ ውህደት" ግምት ውስጥ የከተተ ነው።
ፒዮትር ፓርክሆምቺክ "ወቅቱ በጣም አስቸጋሪ ነው" ነገር ግን የቤላሩስ ባለስልጣናት "ችግሮቹን እየተቋቋሙ ነው" ብለዋል። እንደ እርሳቸው ገለጻ "ተግዳሮቶቹ በበቂ ሁኔታ ተገምግመው ምላሽ ያገኛሉ።"
ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
https://amh.sputniknews.africa/20240718/5761.html
ቤላሩስ የትራክተሮችን ኤክስፖርት ወደ አፍሪካ ለማዞር አስባለች
ቤላሩስ የትራክተሮችን ኤክስፖርት ወደ አፍሪካ ለማዞር አስባለች
Sputnik አፍሪካ
ቤላሩስ የትራክተሮችን ኤክስፖርት ወደ አፍሪካ ለማዞር አስባለች የቤላሩስ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ፒዮትር ፓርክሆምቺክ "የአፍሪካ ሀገራት ገበያዎች ተስፋ ሰጪ እንደሆኑ ተለይተዋል። ድርድሮች እየተካሄዱ ነው፤ ሁሉም ነገር በውጤቱ ላይ የተመሰረተ ነው"... 18.07.2024, Sputnik አፍሪካ
2024-07-18T13:43+0300
2024-07-18T13:43+0300
2024-07-18T14:20+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2024
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий