ኢትዮጵያ የማእድን አቅሟን ለማሳደግ በምታደርገው ጥረት ሩሲያ ቁልፍ አጋር ናት ሲሉ ኢትዮጵያዊው የምጣኔ ሀብት ባለሙያ ተናገሩ

ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ የማእድን አቅሟን ለማሳደግ በምታደርገው ጥረት ሩሲያ ቁልፍ አጋር ናት ሲሉ ኢትዮጵያዊው የምጣኔ ሀብት ባለሙያ ተናገሩ የቀድሞ የተመድ የፖሊሲ ከፍተኛ አማካሪ እና የአፍሪካ ህብረት የሙስና አማካሪ ቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር ቆስጠንጢኖስ በርሄ ተስፉ ከሶቪየት ዘመን ጀምሮ በሩሲያ እና በኢትዮጵያ መካከል በጂኦሎጂካል ፍለጋ ዘርፍ ያለውን የቆየ እና ፍሬያማ ግንኙነት ጠቁመዋል። "ሩሲያ የረጅም ጊዜ የኢትዮጵያ ወዳጅ ነች። እዚህ ሀገር ውስጥ የነበረው የመጀመሪያ እና ብቸኛው የነዳጅ ማጣሪያ በሩሲያውያን የተገነባ ነው" ሲሉ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። አክለውም "ሩሲያ በማዕድን ልማት እና በሌሎች የኢንዱስትሪ ልማት ዘርፎች በምናደርገው እንቅስቃሴ ብዙ ድጋፍ ለማድረግ አቅም አላት" ብለዋል። ሩሲያ በጂኦሎጂካል ፍለጋ በተለይም በኢትዮጵያ ለአሥርተ ዓመታት በነበራት ተሳትፎ ያደበረችውን ሰፊ ዕውቀትና ልምድ አጽንኦት ሰጥተው አንስተዋል። የኢትዮጵያ መንግሥት የሀገሪቱን የማዕድን ሃብት የበለጠ ለማሳደግ የሩሲያን ትብብር በንቃት እንዲፈልግ አሳስበዋል። "የሩሲያ ተቋማት ያላቸውን ከፍተኛ መረጃ በተጨማሪ ጥናት የበለጠ ለማዳበር ሊጠቀሙባቸው ይችላሉ" ብለዋል ዶ/ር ቆስጠንጢኖስ። በተጨማሪም ሩሲያ በምዕራቡ ዓለም ላይ የተጣለውን ማዕቀብ መቋቋም መቻሏን በመግለጽ በአሁኑ ጊዜ አፍሪካን በፋይናንስ የመደገፍ አቅም እንዳላት ገልጸዋል። “ሩሲያ የአፍሪካ ሀገራት እና ኢትዮጵያ የማእድን አቅማቸውን እንዲያጎለብቱ ድጋፍ ለማድረግ አሁን የፋይናንሺያል አቅም አላት። ይህ በመጨረሻ ሁሉን ተጠቃሚ የሚያደርግ ይሆናል ምክንያቱም ማዕድናት ለራሳቸው ይከፍላሉ። የማዕድን ሀብት ባለቤት የሆኑትን ሀገሮች ያበለጽጋሉ" ሲሉ ተናግረዋል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0