እስራኤል በጋዛ በሲቪል ቦታዎች ላይ እያደረሰችው ያላቸው ጥቃት የተኩስ አቁም ጥረቱን ውስብስብ አድርጎታል ስትል ካይሮ ተናገረች

ሰብስክራይብ
እስራኤል በጋዛ በሲቪል ቦታዎች ላይ እያደረሰችው ያላቸው ጥቃት የተኩስ አቁም ጥረቱን ውስብስብ አድርጎታል ስትል ካይሮ ተናገረች “በፍልስጤማውያን ላይ እየደረሰ ያለው የመብት ጥሰት መቀጠሉ፤ የተኩስ አቁም ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት በእጅጉ እንደሚያወሳስበው የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በሰጠው መግለጫ አስታውቋል። በትላንትናው እለት የእስራኤል መከላከያ ሃይል በጋዛ ካን ዩኒስ ከተማ አቅራቢያ በሚገኘው አል ማዋሲ አካባቢ በፈጸመው ዒላማውን የተጠበቀ ጥቃት ከ70 በላይ ሰዎች መገደላቸውን እና ወደ 290 የሚጠጉ ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸው መዘገቡ ይታወሳል። ካይሮ የእስራኤል መንግስት በአል ማዋሲ ላይ ያደረሰውን ጥቃት“በጽኑ ታወግዛለች” እና እስራኤል “የንፁሃን ዜጎችን ህይወት ችላ ማለቷን እንድታቆም” አሳስባለች። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0