ኤለን መስክ ባለፉት ስምንት ወራት ውስጥ ሁለት ሰዎች ሊገድሉት ሞክረው እንደነበር ተናገረ

ሰብስክራይብ
ኤለን መስክ ባለፉት ስምንት ወራት ውስጥ ሁለት ሰዎች ሊገድሉት ሞክረው እንደነበር ተናገረ "ከፊታችን አደገኛ ጊዜ ይጠብቀናል። በሁለት የተለያዩ አጋጣሚዎች ሁለት ሰዎች ሊገድሉኝ ሞክረዋል። ሰዎቹ ቴክሳስ ከሚገኘው ከቴስላ ዋና መስሪያ ቤት በ20 ደቂቃ ርቀት ላይ ከእነ ጦር መሳሪያቸው ተይዘዋል። "ሲል አሜሪካዊው ቢሊየነር በማህበራዊ ሚዲያው ላይ አጋርቷል። በትላንትናው እለት ትራምፕ ንግግር በሚያደርጉበት ወቅት እንደተተኮሰባቸው የሚዲያ የተጋሩ ምሥሎች አሳይተዋል። በኋላም የአሜሪካ የደህንነት አገልግሎት ሠራተኞች ከመድረኩ ላይ ይዘዋቸው ሲወርዱ በቀኝ ጭንቅላታቸው በኩል ደም ይፈስ ነበረ። ትራምፕ በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ መገናኛ ብዙሃኑ ገልፀዋል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0