ዩክሬን ፑቲንን ለመግደል ከአሜሪካን ገንዘብ እንደተቀበለች የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ

ሰብስክራይብ
ዩክሬን ፑቲንን ለመግደል ከአሜሪካን ገንዘብ እንደተቀበለች የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ማሪያ ዛካሮቫ እንደተናገሩት የዩክሬን የጸጥታ አካላት ከአሜሪካን ገንዘብ በመቀበል፤በሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ላይ በርካታ ያልተሳኩ የግድያ ሙከራዎችን አድርገዋል ብለዋል። ይህንን መረጃ መጀመሪያ ያወጣው የዩክሬን ዋና የስለላ ዳይሬክቶሬት ኃላፊ ኪሪል ቡዳኖቭ (Kirill Budanov* )ነው። የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ የፕሬዚዳንት ፑቲን ደህንነት በከፍተኛ ሁኔታ ጥበቃ እንደሚደረግደረጃ ላይ እንደሚገኝ እና ምንም እንኳን ሙከራዎች ቢደረጉም በበቂ ሁኔታ መረጋገጡን አረጋግጠዋል። * ኪሪል ቡዳኖቭ (Kirill Budanov*) በሩሲያ የአሸባሪዎች እና ጽንፈኞች መዝገብ ውስጥ የሰፈረ ግለሰብ ነው። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0