የቡርኪናፋሶ መሪ ፈረንሳይ፣ ቤኒን እና ኮትዲቯር ሀገሪቱን እያተራመሱ ነው ሲሉ ከሰሱ

ሰብስክራይብ
የቡርኪናፋሶ መሪ ፈረንሳይ፣ ቤኒን እና ኮትዲቯር ሀገሪቱን እያተራመሱ ነው ሲሉ ከሰሱ "ከኮትዲቯር ህዝብ ጋር ምንም ችግር የለንም። ኮትዲቯርን እያስተዳደሩ ከሚገኙት ጋር ግን ችግር አለን። ደጋግመን እንናገራለን። በእርግጥም ሀገራችንን ማተራመሻ የኦፕሬሽን ማዕከል በአቢጃን ይገኛል" ሲሉ ኢብራሂም ትራኦሬ ለህዝብ ባደረጉት ንግግር ከሰዋል። በተጨማሪም ቡርኪናፋሶ በምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ላይ ያነጣጠሩ ሁለት የፈረንሳይ ጦር ሰፈሮች በቤኒን እንደሚገኙ የሚያሳይ ማስረጃ አላት ብለዋል። ሆኖም የፈረንሳይ ጦር ቤኒን የጦር ሰፈሮች የሉኝም ሲል ለቱርክ የመንግሥት ሚዲያ አናዶሉ ኤጀንሲ በሰጠው አስተያየት ክሱን በይፋ ውድቅ አድርጓል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0