ኤርዶኦን የጥቁር ባህር እህል ኢኒሼቲቭ በድጋሚ ይጀመራል ብለው ተስፋ እንደሚያደርጉ ገለፁ

ሰብስክራይብ
ኤርዶኦን የጥቁር ባህር እህል ኢኒሼቲቭ በድጋሚ ይጀመራል ብለው ተስፋ እንደሚያደርጉ ገለፁ "የጥቁር ባህር እህል ኢኒሼቲቭን እንከታተላለን። የዶልማባቼ ሂደት (በኢስታንቡል ድርድር የተካሄደበት እና በጥቁር ባህር እህል ኢኒሼቲቭ ዙርያ ስምምነት የተፈረመበት) ይጎለብታል ብለን እናስባለን። ተስፋችን ነው" ሲሉ ኤርዶአን በዋሽንግተን ጋዜጣዊ መግለጫ በሰጡበት ወቅት ገልጸዋል። በሐምሌ ወር መጀመሪያ ኤርዶአን በካዛክስታን አስታና ከሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ተገናኝተው በቱርክ በኩል በችግር ላይ ላሉ አፍሪካ ሀገራት አዲስ "የእህል ኮሪደር" የመፍጠር ሀሳብ ላይ መወያየታቸውን ተናግረዋል። ከዚህ በተጨማሪ የቱርኩ መሪ አንካራ የሻንጋይ የትብብር ድርጅት ቋሚ አባል ሀገር የመሆን እቅድ እንዳላት ገልጸዋል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0