የሐምሌ 05 ረፋድ ዋና ዋና የዓለም ዜናዎች፡-

ሰብስክራይብ
የሐምሌ 05 ረፋድ ዋና ዋና የዓለም ዜናዎች፡- 🟠 የኬንያው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ የታክስ ጭማሪውን ተከትሎ በተነሳው ተቃውሞ ምክንያት ካቢኔያቸውን መበተናቸውን አስታወቁ። በምላሹ አይ.ኤም.ኤፍ በኬንያ ውስጥ ያለውን ፕሮግራም እየገመገመ እንደሆነ ገልጿል። 🟠 የደቡብ አፍሪካ ልማት ማህበረሰብ የፖለቲካ፣ መከላከያ እና ፀጥታ ትብብር አካል 26ኛ የሚኒስትሮች ደረጃ ስብሰባ በዛምቢያ እየተካሄደ ነው። 🟠 በደቡብ አፍሪካ ያጋጠመው ከባድ አውሎ ንፋስ እና ዝናብ 4,500 የሚጠጉ ሰዎችን ቤት አልባ አድርጓል። አንድ የመርከብ ኩባንያ በአፍሪካ ደቡባዊ ጫፍ አካባቢ የባህር ላይ ጉዞ የመርከብ አደጋ ሊያስከትል እንደሚችል አስጠንቅቋል፡፡ 🟠 የዩክሬን ሰው አልባ አውሮፕላኖች በቤልጎሮድ ክልል ሸቤኪኖ ባደረሱት ጥቃት ጉዳት ከደረሰባቸው አምስት ህጻናት መካከል ሁለቱ በከባድ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙና የቀዶ ህክምና እየተደረገላቸው መሆኑን የክልሉ ጤና ሚኒስትር አንድሬ ኢኮኒኮቭ አስታውቀዋል። 🟠 አውስትራሊያ ትልቁን የነጠላ ወታደራዊ ዕርዳታ 250 ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ ለኪዬቭ እንደምትሰጥ አስታውቃለች (በአጠቃላይ ወደ 1.1 ቢሊዮን ዶላር ተጠግቷል)። 🟠 የኔቶ ዋና ፀሃፊ በኪዬቭ የዩክሬን ባለስልጣናትን የሚያስተባበር ከፍተኛ ተወካይ ለመሾም ወሰኑ፡፡ 🟠 ቱርክ የሻንጋይ የትብብር ድርጅት ቋሚ አባል ለመሆን አንደምታስብ ፕሬዝዳንት ኤርዶአን ተናግረዋል። 🟠 የሃንጋሪ ጠቅላይ ሚኒስትር እና የቀድሞ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ትራምፕ በማር-አ-ላጎ ርስት ተገናኝተዋል። ኦርባን ትራምፕ የዩክሬን ግጭት "ጉዳዮችን ይፈታሉ" ብለዋል፡፡ 🟠 በኔቶ ስብሰባ ባይደን ምላሳቸው ሳት ብሎ በስህተት በዘለንስኪ ምትክ መድረኩን ለ"ፕሬዝዳንት ፑቲን" አስረክበዋል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0