ቡርኪናፋሶ ከኢኮዋስ የወጣችው በዘመናዊ ቅኝ አገዛዝ ራዕዩ ምክንያት ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናገሩ

ሰብስክራይብ
ቡርኪናፋሶ ከኢኮዋስ የወጣችው በዘመናዊ ቅኝ አገዛዝ ራዕዩ ምክንያት ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናገሩ ጠቅላይ ሚኒስትር አፖሊኔየር ኪየለም ዴ ታምቤላ "ከኢኮዋስ ከመውጣታችን በፊት፤ ሀገሮቻችን ከኢኮዋስ በፊትም ነበሩ ያለ ስብስቡም ሊኖሩ ይችላሉ ብዬ ነበር። የአፍሪካ ህብረትንም እየተመለከትን ነው፣ የኢኮዋስን ዓይነት ባህሪ የሚያሳይ ከሆነ እንተወዋለን፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅትም ከዚህ ውጪ አይደለም" ማለታቸውን ጽህፈት ቤታቻው ጠቅሷል። አክለውም የቡርኪናፋሶ ህዝብ ከቅኝ ግዛት በፊት ከምዕራቡ ዓለም ጋር ምንም አይነት ግንኙነት ሳይኖረው ስኬታማ ነበር ብለዋል። በተመሳሳይ እንደ ታይላንድና ኢትዮጵያ ያሉ ሀገሮች በቅኝ ተገዝተው ባያውቁም እያደጉ ነው። በአንጻሩ ምዕራባውያን ናቸው አንዳንድ ሀገራትን በማያቋርጥ ጭቆና ለመያዝ "መውጫ በሌለው መረብ" የሚጠልፉት። እንደ ኪየለም ዴ ታምቤላ ቡርኪናፋሶ የግዛት እንድነቷን ለማስጠበቅ እና ለዕድገቷ የምታደርገውን ትግል የሚያስቆም ምንም ነገር አይኖርም። "ከ1960 ጀምሮ ስለ ዕርዳታ እያወራን እድገት አላየንም፣ አልተቀሳቀስንም። ስለ ልማት ድጋፍ፣ ስለ ትብብር ድጋፍ እናወራለን ከ1960 ጀምሮ ግን አላደግንም። ይህን ዓይነቱን እርዳታ ልንጠራጠር ይገባል” ሲሉም አክለዋል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0