ልዩ ቃለመጠይቅ| የኢትዮጵያ ፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ በሩሲያ እና በኢትዮጵያ ፓርላማዎች መካከል ያለውን "ጠንካራ ግንኙነት" አደነቁ

ሰብስክራይብ
ልዩ ቃለመጠይቅ| የኢትዮጵያ ፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ በሩሲያ እና በኢትዮጵያ ፓርላማዎች መካከል ያለውን "ጠንካራ ግንኙነት" አደነቁ አገኝሁ ተሻገር "በሩሲያ እና ኢትዮጵያ ፓርላማዎች እንዲሁም በብሪክስ ፓርላማዎች እና ሌሎች ፓርላማዎች ጋር ጥሩና ጠንካራ ግንኙነት በመፈጠሩ ደስተኞች ነን" ሲሉ ከብሪክስ የፓርላማ መድረክ ጎን ለጎን ለስፑትኒክ ተናግረዋል። እንደ አፈ-ጉባዔው ገለጻ ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በመከላከያ፣ ማእድንና ሌሎች ዘርፎች ትምህርትንም ጨምሮ 22 የሚጠጉ ስምምነቶችን ተፈራርመዋል። ከእነዚህ ውስጥ 14 ያህሉ ጸድቀዋል። "በፓርላማዎቹ መካከል በአቅም ግንባታ፣ የቴክኒክ ድጋፍ [እና በሌሎች ጉዳዮች] ትብብር መኖሩ ለሁለቱ ሀገራት እንዲሁም ለሌሎች ሀገራት በተለይም ለብሪክስ ሀገራት ፓርላማ አባላት ትልቅ ጠቀሜታ ይኖረዋል" ሲሉም አፈ-ጉባዔው አስምረዋል። አክለውም ሁለቱ ሀገራት "ሰላም፣ አመራርና የተለያዩ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴዎችን በሚመለከት ግንኙነት ሊኖራቸው ይገባል" ብለዋል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0