የሐምሌ 2 የዓለም ዋና ዋና ዜናዎች

ሰብስክራይብ
የሐምሌ 2 የዓለም  ዋና ዋና ዜናዎች 🟠 ቭላድሚር ፑቲን የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲን በሞስኮ መቀበላቸውን ቀጥለዋል። ኦፊሴላዊ የሩሲያ-ህንድ ውይይቶች ዛሬ ይደረጋሉ። ስብሰባው በተወሰነ እና ሰፋ ባለ ቅርፅ ይከናወናል። 🟠 38 የዩክሬን አውሮፕላኖች በሩሲያ ቤልጎሮድ፣ ኩርስክ፣ ቮሮኔዝ፣ ሮስቶቭ እና አስትራካን ክልሎች ባንድ ሌሊት እንደወደሙ የሀገሪቱ የመከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል። 🟠 ጠቅላይ ሚኒስትር ቪክቶር ኦርባን ወደ ኪየቭ፣ ሞስኮ እና ቤጂንግ ጉዞ እያደረጉ ባሉበት ወቅት የአውሮፓ ህብረት አምባሳደሮች የሀንጋሪን የህብረቱ ሊቀመንበርነት የተመለከተ ውይይት ረቡዕ እንደሚያደርጉ ዩራክቲቭ የዜና ድረ-ገፅ ዘግቧል። 🟠 የፈረንሳይ አቃቤ ህጎች የ2022 ፕሬዝዳንታዊ የምርጫ ዘመቻን በሕገ-ወጥ ገንዘብ ፋይናንስ አድርገዋል በሚል በተጠረጠሩት ፖለቲከኛዋ ማሪን ለፔን ላይ ምርመራ ጀመሩ። 🟠 የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ባይደን ሀገራቸው እና አጋሮቿ የዩክሬንን የአየር መከላከያ ስርዓት ለማጠናከር አዳዲስ እርምጃዎችን እንደሚወስዱ ተናገሩ። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0