ኬንያ በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን 80 በመቶ የሚሆነውን የመንግስት አገልግሎት በኦንላየን (Online ) ሥርዓት ለመስጠት አቅዳለች

ሰብስክራይብ
ኬንያ በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን 80 በመቶ የሚሆነውን የመንግስት አገልግሎት በኦንላየን (Online ) ሥርዓት ለመስጠት አቅዳለች የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን፣ ቴክኖሎጂ (አይሲቲ) ፣ ኢ-ገቨንመንት እና ዲጂታል ኢኮኖሚ ፀሃፊ የሆኑት ሜሪ ከሬማ እንዳስታወቁት፤ ይህ ትልቅ እቅድ በኬንያ አሁን ባለው የዲጂታል መሠረተ ልማት ላይ የተገነባ ሲሆን በ eCitizen ፕላትፎርም በመስመር አማካኝነት 17,000 የኦንላየን አገልግሎቶች እየተሰጡ ይገኛሉ። ይህ አጋርነት በፓዮኒር ዓለም አቀፍ ዩኒቨርሲቲ (Pioner International University ) በተዘጋጀው 'ኮንቬርጀንስ እና ስማርት ሲስተምስ'በተሰኘ ስብሰባ ላይ ውይይት ተደርጎበታል። ከሬማ በአይሲቲ በመታገዝ በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ መሪ ለመሆን ሀገሪቱ ያላትን ከፍተኛ ገለፀው፤ መንግስት ዜጎችን ከሳይበር ጥቃት ለመከላከል ማዕቀፎችን በንቃት እየሰራ ይገኛል ብለዋል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0