አለም በምዕራባውያን ልሂቃን ጫና እና ዳግም-ቅኝ ገዢዎች ምኞት ተሰላችቷል ሲሉ በቻይና የሩሲያ አምባሳደር ተናገሩ።

ሰብስክራይብ
አለም በምዕራባውያን ልሂቃን ጫና እና ዳግም-ቅኝ ገዢዎች ምኞት ተሰላችቷል ሲሉ በቻይና የሩሲያ አምባሳደር ተናገሩ። በዛሬው ዕለት በቤጂንግ እየተካሄደ ባለው 12ኛው የአለም የሰላም ፎረም ላይ አምባሳደር ኢጎር ሞርጉሎቭ እንዳሉት እውነተኛ ስትራቴጂካዊ ነፃነትን የሚፈልጉ ሀገራት ቁጥር  ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል ብለዋል። በዝግጅቱ ላይ የሩሲያው ዲፕሎማት የተናገሯቸው ሌሎች ቁልፍ ሃሣቦች ከዚህ በታች ቀርበዋል። 🟠 ሩሲያ እና የብሪክስ ሀገራት ከሶስተኛ ወገኖች የበላይነት ነፃ የሆነ የፋይናንስ ስርዓት እየፈጠሩ ነው 🟠 የብሪክስ ምኞት የምዕራባውያንን የበላይነት ሚዛን ለማስጠበቅ ያለመ እና ሌላ የበላይነት ስልት ለመፍጠር ያለመ አይደሉም። 🟠 የብሪክስ ሀገራት የጋራ ገንዘብ ለመፍጠር እየተነጋገሩ ነው። የጋራ ገንዘብ በቅርብ ጊዜ ውስጥ መፍጠር የማይቻል ቢሆንም ፤በጉዳዩ ዙሪያ በተጨባጭ እየተንቀሳቀስ ነው። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0