የህንዱ መሪ ሩሲያን በሚጎበኙበት ወቅት ለትንሽ ጊዜም ቢሆን ከፑቲን ጋር እንደሚወያዩ ክሪምሊን ገልጿል።

ሰብስክራይብ
የህንዱ መሪ ሩሲያን በሚጎበኙበት ወቅት ለትንሽ ጊዜም ቢሆን ከፑቲን ጋር እንደሚወያዩ ክሪምሊን ገልጿል። የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ እ.አ.አ ከሐምሌ 8-9 በሩሲያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ያደርጋሉ። "ይህ ይፋዊ ጉብኝት ይሆናል።እናም የሁለቱ ሀገራት መሪዎች መደበኛ ባልሆነ ሁኔታ እንደሚወያዩ ተስፋ እናደርጋለን። እና በእርግጥ ድርድሩ በተጣበበ ሁኔታም ቢሆን በክሬምሊን ይደረጋል።ሰፋ ያለው ድርድር ግን ከሌሎች የልዑካን ቡድን አባላት ጋር ይካሄዳል"ሲሉ የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ ተናግረዋል። ሞስኮ ለሁለቱ ሀገራት ግንኙነት አስፈላጊ የሆነው የሞዲ ጉብኝት በባህሪው የተሟላ እንደሚሆን ትጠብቃለች ብለዋል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0