የቀድሞ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ፔዜሽኪያን የኢራንን ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ማሸነፈቸውን የምርጫ ኮሚሽን አስታውቋል

ሰብስክራይብ
የቀድሞ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ፔዜሽኪያን የኢራንን ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ማሸነፈቸውን የምርጫ ኮሚሽን አስታውቋል የኢራን ምርጫ ኮሚሽን ቃል አቀባይ ሞህሰን ኢስላሚ እንደተናገሩት የኢራን ሁለተኛ ዙር ፕሬዚዳንታዊ ምርጫን የቀድሞው የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ማሱድ ፔዜሽኪያን ማሸነፋቸውን ገልጿል። "ማሱድ ፔዜሽኪያን 16,384,403 ድምፅ እንዲሁም የቀድሞው የኒውክሌር ተደራዳሪ ሰኢድ ጃሊሊ ደግሞ 13,538,179 ድምፅ አግኝተዋል" ሲል የኤስ ኤን ኤን የዜና አገልግሎት ኢስላሚን ጠቅሶ ዘግቧል። 30,573,931 ህዝብ ድምጽ መሥጠቱን ገልጸው፤ በምርጫው የመራጮች ተሳትፎ 49.8 በመቶ መድረሱን ተናግሯል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0