የኬንያ ፕሬዝዳንት በተቃውሞ ሰልፉ ሳቢያ ያለውን የበጀት ጉድለት ለማካካስ በሚል 47 የመንግስት መስሪያ ቤቶች እንዲታጠፉ እና የኃላፊነት የስራ ቦታዎች እንዲቀነሱ አዘዙ።

ሰብስክራይብ
የኬንያ ፕሬዝዳንት በተቃውሞ ሰልፉ ሳቢያ ያለውን የበጀት ጉድለት ለማካካስ በሚል 47 የመንግስት መስሪያ ቤቶች እንዲታጠፉ እና የኃላፊነት የስራ ቦታዎች እንዲቀነሱ አዘዙ። "ተደራራቢና የሆነ ተግባር ያላቸው 47 የመንግስት ኮርፖሬሽኖች ይፈርሳሉ፣ በዚህም የሥራ ማስኬጃ እና የጥገና ወጪያቸው ይቀነሳል፣ ተግባራቸውም በየሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶቻቸው ውስጥ እንዲካተት ይደረጋል" ሲሉ ሩቶ ለሀገሪቱ ህዝቦች ባደረጉት ንግግር ላይ ተናግረዋል። ፕሬዚዳንቱ በመቀጠል "በመንግስት ውስጥ ያሉ የአማካሪዎች ቁጥር በ 50 በመቶ ወዲያውኑ ይቀንሳል ብለዋል።" ከዚህም በላይ ለባለሥልጣናት ዓለም አቀፍ ጉዞዎች ለአንድ ዓመት ያህል እንዲታገድ ሲወስኑ  የሕግ አውጭ አካላት ለህዝቦቻቸው ገንዘብ የሚሰጡበትን ዓመታዊ "ሀራምቤዎች" የተሰኘውን ሁነትንም አግደዋል ። ሩቶ ብሔራዊ ዕዳን ኦዲት የሚያደርግ ግብረ ኃይል መቋቋሙን ገልጾ፣ 346 ቢሊዮን የኬንያ ሽልንግ (2.69 ቢሊዮን ዶላር) መበደር፤ ለሀገሪቱ ገበሬዎች የሚደረገውን የበጀት ቅነሳን ያስቀራል  ሲሉ ተከራክሯል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0