የደቡብ አፍሪካ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ዙማ ፓርቲ ከምርጫ ውዝግብ ጋር በተያያዘ አስገብቶት የነበረውን ክስ አነሳ

ሰብስክራይብ
የደቡብ አፍሪካ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ዙማ ፓርቲ ከምርጫ ውዝግብ ጋር በተያያዘ አስገብቶት የነበረውን ክስ አነሳ የኡምኮቶዊዝዌ(ኤም ኬ)ፓርቲ የህግ አማካሪ በምርጫ ኮሚሽኑ ላይ ያቀረቡትን ቅሬታ እንዲያቋርጡ ማሳሰቢያ ሰጥተዋል፤ ፓርቲው ምርጫው ነፃ እና ፍትሃዊ አይደለም በሚል በምርጫ ፍርድ ቤት ክስ አቅርቦ ነበር። ከፍተኛ ፉክክር በተደረገበት ምርጫ፣ ከአንድ አመት በፊት የተመሰረተው አም ኬ ፓርቲ 58 መቀመጫዎችን በመያዝ በ ፓርላማው ብዙ መቀመጫዎችን በመያዝ በሶስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።የሲሪል ራማፎሳን ድል በመቃወም የመክፈቻውን ሥነ ሥርዓትም አልተካፈለም፤ የፓርቲው የፓርላማ ተወካዮች ኋላ ላይ ግን ቃለ መሃላ ፈጽመው ፓርላማውን ተቀላቅለዋል። ከዚህ ቀደም ዙማ ሲመሩት የነበረው የአፍሪካ ብሄራዊ ኮንግረስ (ኤኤንሲ) እ.ኤ.አ ከ1994 ጀምሮ ለመጀመሪያ ጊዜ በፓርላማ አብላጫውን ወንበር አጥቷል። 40.18% የሆነውን ድምጽ ብቻ ከማግኘቱ በተጨማሪ የተወሰኑ ግዛቶችንም ድምፅ አጥቷል። በውጤቱም ኤኤንሲ 11 ከሚሆኑ ሌሎች ፓርቲዎች ጋር በመሆን የብሄራዊ አንድነት መንግስት ማቋቋሙ ይታወሳል። ኤም ኬ ፓርቲ ግን የአንድነት መንግስቱን አልተቀላቀለም። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0