የኬንያ ማዕከላዊ ባንክ ኤክስፐርት የብድር አስተዳደር መምሪያን በኃላፊነት ሊመሩ ነው

ሰብስክራይብ
የኬንያ ማዕከላዊ ባንክ ኤክስፐርት የብድር አስተዳደር መምሪያን በኃላፊነት ሊመሩ ነው ኬንያ የማዕከላዊ ባንክ ኢኮኖሚስት ራፋኤል ኦዊኖን የዕዳ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ አድርጎ መሾሟን የሀገሪቱ የፋይናንስ ሚኒስቴር ረቡዕ ዕለት አስታውቋል። ኦዊኖ በጥር ወር ከስልጣን የለቀቁትን ሃሮን ሲሪማ ተክተዋል። የፋይናንስ ሚኒስቴሩ ኦዊኖ በሕዝብ ዕዳ አስተዳደር ፣የእዳ ደረጃን ወጥ አስተማማኝ በሆነ መንገድ ማስቀጠል፣የረጅም ጊዜ የአገልግሎት ወጪን በመቀነስ እና የተጠባባቂ እዳዎችን ማስተዳደርን ጨምሮ በሕዝብ አስተዳደር ያላቸውን እውቀት ሚኒስቴር አድንቋል። የቢሮው ለውጦች እየታዩ ያሉት የሀገሪቱን ዕዳ ለመቆጣጠር እየተወሰዱ ባሉ እርምጃዎች እንዲሁም የዊሊያም ሩቶ የግብር ጭማሪ ጋር በተያያዘ ነው። ቀደም ሲል የታክስ ጭማሪ ሃሳብን ተከትሎ በመላ ሀገሪቱ የተቀሰቀሰው ሁከትና ብጥብጥ የታክስ ጭማሪ ህጉ እንዲቀር ማድረጉ ይታወሳል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0