በኢትዮጵየ የዋጋ ግሽበት ከ30% ወደ 23% መቀነሱን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገለፁ

ሰብስክራይብ
በኢትዮጵየ የዋጋ ግሽበት ከ30% ወደ 23% መቀነሱን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገለፁ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ይህን ያሉት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ማብራሪያና ምላሽ ሲሰጡ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚህ ዓመት መንግስት 529 ቢሊየን ብር ገቢ ለመሰብሰብ አቅዶ ባለፉት 11 ወራት 466 ቢሊየን ብር ገቢ እንደሰበሰበም አንስተዋል። የተለያዩ ሀገራትን የግብር አሰባበሰብ ልምድ ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ከጂዲፒዋ 7% ብቻ ግብር እንደምትሰበስብ ተናግረዋል፡፡ ይህንን ቁጥር ወደ 10% ከፍ ማድረግ ለሚነሱ የልማት ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት እንደሚረዳም አንስተዋል፡፡ የፋይናንስ ሴክተሩ በበርካታ አመላካቾች ጤናማ ሂደት ውስጥ ይገኛል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባንኮች ከሚያቀርቡት ብድር ከ80% በላይ የግሉ ዘርፍ ተጠቃሚ ነው ብለዋል፡፡ ይህም የፋይናንስ ዘርፉ በጤናማ እንቅስቃሴ ላይ መሆኑን እንደሚያረጋግጥ ገልጸዋል፡፡ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0