የብሪክስ ዓለም አቀፍ ጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት ድርሻ በ2023 ጨምሮ 35.

ሰብስክራይብ
የብሪክስ ዓለም አቀፍ ጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት ድርሻ በ2023 ጨምሮ 35.7% ደርሰ የዓለም ባንክ መረጃን መሰረት ያደረገው የስፑትኒክ ስሌት የቡድን ሰባት ኢኮኖሚያዊ አመላካቾች ወደ 29% መውረዱን አሳይተዋል። በ2023 መገባደጃ ብሪክስ በዓለም አቀፍ ምርት ውስጥ ያለው ድርሻ ከዓመት ዓመት በ0.6% ነጥብ አድጓል። ስብስቡ እ.አ.አ በ2006 ከተመሰረተ በኋላ በዓለም ኢኮኖሚ ላይ ያለው ድርሻ በ10.2% ጨምሯል፡፡ በተመሳሳይ የቡድን ሰባት ድርሻ ባለፉት ዓመታት በ0.4% ነጥብ ቀንሷል። ከ2006 ጀምሮ ድርሻው በ9.7% ወርዷል። በመግዛት አቅም እኩልነት የዓለም ጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት በ2023 184.7 ትሪሊዮን ዶላር የደረሰ ሲሆን ይህም ከአንድ ዓመት በፊት ከነበረው 7% ጭማሬ አሳይቷል። የተቀረው ዓለም ባለፈው ዓመት 35.3% የዓለም ጂዲፒን የሚሸፍን ሲሆን ይህ ድርሻ እ.አ.አ ከ1990 ጀምሮ በአንድ መቶኛ ነጥብ እየተለወዋጠ በአብዛኛው የተረጋጋ ሆኖ ቆይቷል፡፡ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0