የኬንያ ተቃዋሚ ፓርቲ የናይሮቢን ማህበራዊ አለመረጋጋት ተከትሎ አስቸኳይ ምርጫ እንዲካሄድ ጠየቀ

ሰብስክራይብ
የኬንያ ተቃዋሚ ፓርቲ የናይሮቢን ማህበራዊ አለመረጋጋት ተከትሎ አስቸኳይ ምርጫ እንዲካሄድ ጠየቀ የኬንያ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ጥምረት አዚሚዮ ከፀረ-መንግሥት ሰልፉ አኳያ ፕሬዝዳንት ዊልያም ሩቶ በ2024 ምርጫ ማዕቀፍ የገለልተኛ ኮሚሽን ህጉን ፈርመው የቅድሚያ ምርጫ ዝግጅት እንዲደረግ አሳስቧል። "ሁሉም ኬንያውያን አንድ እንዲሆኑ ጥሪያችንን እናቀርባለን። [...] ሩቶ ለድርጊቶቹ ሀላፊነት የሚወስድበት ጊዜ አሁን ነው። በእጁ ላይ ደም ስላለ ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር እንዲካሄድ መፍቀድ አለበት" ብለዋል የዋይፐር ዴሞክራቲክ ንቅናቄው መሪ ካሎንዞ ሙሲዮካ። መንግሥት ሰላማዊ ሰልፉን የብሔራዊ ደህንነት ስጋት እንደሆነ አድርጎ ለማቅረብ በንብረት ላይ ጉዳት ያደረሱ የተቃውሞ ቀስቃሾችን ስፖንሰር አድርጓል ሲሉም ከሰዋል። ባለፈው ሳምንት ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ህዝባዊ ቁጣውን ተከትሎ የፋይናንስ ህግ 2024ትን አንስተዋል። በሀገሪቱ ስርዓት ​​ለመመለስ ቃል የገቡ ሲሆን ወጣቶችም የአስተዳደር ጉዳዮችን በተመለከቱ ውይይቶች ተሳትፎ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል። በተቃውሞ ሰልፉ 39 ኬንያውያን ሲገድሉ 300 የሚሆኑት ላይ ደግሞ ጉዳት እንደደረሰ የኬንያ ብሔራዊ የሰብአዊ መብት ኮሚሽን የቅርብ መረጃ አመልክቷል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0