የኬንያ ፖሊስ በማክሰኞው ህዝባዊ ተቃውሞ በወንጀል ድርጊት የተሳተፉ ከ270 በላይ ሰዎችን እንደያዘ ገለፀ

ሰብስክራይብ
የኬንያ ፖሊስ በማክሰኞው ህዝባዊ ተቃውሞ በወንጀል ድርጊት የተሳተፉ ከ270 በላይ ሰዎችን እንደያዘ ገለፀ በተለያዩ የሀገሪቱ ከተሞች በወጣቶች መሪነት በተካሄደው ሰልፍ ከፍተኛ ዘረፋ እና የንብረት ውድመት እንደደረሰ የተዘገበ ሲሆን ሰልፉ ላይ "ተቀጣሪ ወሮበሎች" ሰርገው ገብተው እንደነበር አንዳንድ ተቃዋሚ ሰልፈኞች ተናግረዋል። የወንጀል ምርመራ ዳይሬክቶሬት በኤክስ የማህበራዊ ገፁ በለጠፈው መግለጫ “በመላው ሀገሪቱ የሚገኙ የጸጥታ ሃይሎች የተቃውሞ ሰልፈኛ በመምሰል በወንጀል ድርጊት ሲሳተፉ የተገኙ ተጠርጣሪዎችን ለይተው አስረዋል" ብሏል በአጠቃላይ 204 ተጠርጣሪዎች በዋና ከተማዋ ናይሮቢ እና ሌሎች 68 የሀገሪቱ አካባቢዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውንም ገልጿል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0