በምስራቅ ጎጃም ዞን ደጀን ወረዳ ሁለት የፖሊስ አዛዦች በጥይት ተገደሉ

ሰብስክራይብ
የወረዳው ኮሚዩኒኬሽን በማህበራዊ ትስስር ገፁ ባወጣው መግለጫ አብሯቸው መኪና በማሽከርከር ላይ የነበረ አንድ የፖሊስ አባል ቆስሎ ህክምና እየተደርገለት እነደሚገኝ ገልጧል፡፡የፖሊስ አዛዦቹ ላይ ጥቃቱ የተከፈተባቸው ትላንት ከቀኑ 8፡ዐዐ ሰዓት አካባቢ በደጀን ወረዳ ኩራር ቀበሌ ደምበዛ ጎጥ የሚሰጠውን የ8ኛ ክልላዊ ፈተና የጸጥታ ስራ ለመከታተል በወጡበት መሆኑን የወረዳው አስተዳደር ገልጧል፡፡ አስተዳደሩ ወንጀለኞቹን በአጭር ጊዜ ለህግ ለማቅረብ ጠንክሮ የሚሰራ መሆኑን አስታውቋል፡፡ህይወታቸውን ላጡት አዛዦች የተሰማውን ሀገን የገለፀው የወረዳው አስተዳደር ምክር ቤት፣ የህዝብ ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ ሲሉ መስዋዕት የሆኑ የፀጥታ አካላት ቤተሰቦችን አስተዳደሩ እንደራሱ አድርጐ የሚንከባከብና የሚደግፍ ይሆናል ሲል አስታውቋል፡፡
አዳዲስ ዜናዎች
0