ቱርክ ጠበኞቹን ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ሸመገለች

ሰብስክራይብ
ቱርክ ጠበኞቹን ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ሸመገለች የሶማሊያ እና ኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች አህመድ ሙአሊም ፊቂ እና ታዬ አፅቀስላሴ በሀገሮቻቸው መካከል የሚነሱ አከራካሪ ጉዳዮችን ለመፍታት በአንካራ ተወያይተዋል። ውይይቱ በኢትዮጵያ እና ሶማሊላንድ መኻከል የተደረሰውን የባህር በር ስምምነት እንደሚመለከት ተገልጿል። የሶማሊያ መንግሥት ስምምነቱ የሀገሪቱን ሉዓላዊነት እንደጣሰ አድርጎ ይመለከተዋል። በሌላ በኩል የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ሀገራቸው ከሶማሊያ ጋር ግጭት የመፍጠር ዓላማ እንደሌላት እና የባህር መዳረሻ ፍላጎቶቿን ማሟላት ላይ ብቻ ትኩረት ሰጥታ እየሰራች እንደሆነ ተናግረዋል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0