ከ2024 መጀመሪያ ጀምሮ በምስራቅ እና በደቡብ አፍሪካ ከፍተኛ የኮሌራ ወረርሽኝ ተከስቷል ተባለ

ሰብስክራይብ
ከ2024 መጀመሪያ ጀምሮ በምስራቅ እና በደቡብ አፍሪካ ከፍተኛ የኮሌራ ወረርሽኝ ተከስቷል ተባለ "እ.አ.አ ከጥር 2024 እስከ መጋቢት 2025 ድረስ በምስራቅ እና በደቡብ አፍሪካ በሚገኙ 16 ሀገራት ከ178 ሺህ በላይ ሰዎች በኮሌራ ተይዘዋል" ሲል የተባበሩት መንግሥታት የሕፃናት መርጃ ድርጅት (ዩኒሴፍ) አስታውቋል። በውሃ፣ ንጽህና፣ ጤና ጥበቃ እና በጤና አገልግሎቶች ውስንነት ምክንያት በሽታው በመባባሱ 2 ሺህ 900 የሚጠጉ ሰዎች፤ አብዛኛቹ ህጻናት መሞታቸውን ዩኒሴፍ ጨምሮ ገልጿል። በደቡብ ሱዳን 50 በመቶ እንዲሁም በአንጎላ 40 በመቶ ከ15 ዓመት በታች እድሜ የሆኑ ህጻናት በበሽታው እንደተያዙና በእነዚህ ሁለት ሀገራት ያለው የኮሌራ ወረርሽኝ የከፋ እንደሆነ ድርጀቱ ጠቁሟል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ@sputnik_ethiopia መተግበሪያ | X ላይ ይከተሉን
አዳዲስ ዜናዎች
0