ሞስኮ የኪዬቭ ወታደሮች በሩሲያ ጋዜጠኞች ላይ የሚፈጽሙትን ግድያ ዓለም እንዲያወግዝ ጥሪ አቀረበች

ሰብስክራይብ
ሞስኮ የኪዬቭ ወታደሮች በሩሲያ ጋዜጠኞች ላይ የሚፈጽሙትን ግድያ ዓለም እንዲያወግዝ ጥሪ አቀረበች የሩሲያው ጋዜጣ ኢዝቬስቲያ እና ዝቬዝዳ የዜና ማሠራጫ ጋዜጠኞቻቸው በልዩ ወታደራዊ ኦፕሬሽኑ አካባቢዎች በዩክሬን ጥቃት መገደላቸውን ሰኞ እለት አስታወቀዋል፡፡ የኢዝቬስቲያ ዘጋቢ አሌክሳንደር ፌዶርቻክ የዝቬዝዳ የካሜራ ባለሙያ ፓኖቭ የቀረጻ ቡደን ሹፌር አሌክሳንደር ሲርኬሊ ዘጋቢ ኒኪታ ጎልዲን ከባድ ጉዳት የደረሰባት የሉሃንስክ ህዝቦች ሪፐብሊክ ኃላፊ ሊዮኒድ ፓሴችኒክ የዩክሬን ጦር በክሬሜንስኪ አካባቢ በፈጸመው ጥቃት ሶስት የሚዲያ ሠራተኞችን ጨምሮ ስድስት ሰዎች መገደላቸውን ተናግረዋል። "ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ፣ ዓለም አቀፍ የጋዜጠኞች ሙያዊ ማህበራት እና የሚዲያ ተወካዮች በዘለንስኪ አገዛዝ የተፈጸሙትን እነዚህን እና ሌሎች አሰቃቂ ወንጀሎች አጥብቀው እንዲያወግዙ እና የዩክሬን የጦር ኃይሎች የሚዲያ ባለሙያዎችን ጨምሮ ንፁሀኖች ላይ የሚያደርሱትን ጥቃት በአስቸኳይ እንዲያቆሙ ግፊት እንዲያደርጉ እንጠይቃለን" ሲሉ የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ማሪያ ዛካሮቫ ተናግረዋል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ@sputnik_ethiopia መተግበሪያ | X ላይ ይከተሉን
አዳዲስ ዜናዎች
0