ጃፓን በሀገሪቱ የተከሰተውን የሰደድ እሳት ለማጥፋት ሠራዊቷን አሠማራችየጃፓን የምድር ኃይሎች በምዕራባዊ ግዛቶች በኦካያማ እና ኢሂሜ የእሳት አደጋ መከላከል ሥራዎችን እንደተቀላቀሉ የጃፓን ዋና የካቢኔ ፀሐፊ ዮሺማሳ ሃያሺ ተናግረዋል። ሰደድ እሳቱ እሁድ ዕለት ከተነሳ በኋላ በግዛቱ አስተዳዳሪዎች ጥያቄ መሠረት እርዳታ እንደተላከ ሃያሺ አክለዋል። ወደ 2 ሺህ 700 የሚጠጉ ነዋሪዎች አካባቢውን እንዲለቁ ትዕዛዝ እንደተሰጣቸው ባለስልጣኑ ገልፀዋል። የእሳት ቃጠሎው በኢሂሜ 128 ሄክታር በኦካያማ ደግሞ በ250 ሄክታር ላይ ተስፋፍቷል ብለዋል። በጃፓን የመጨረሻው ትልቁ የእሳት ቃጠሎ በሰሜን ምስራቅ ኢዋቴ ግዛት በምትገኘው ኦፉናቶ ከተማ ለ12 ቀናት የዘለቀ ነበር፡፡ ወደ 3 ሺህ ሄክታር ወይም 9 በመቶ የሚሆነውን የከተማዋን አጠቃላይ ስፍራ ያወደመ ሲሆን ባለስልጣናት 4 ሺህ 500 ሰዎች አካባቢውን እንዲለቁ ትዕዛዝ እንደሰጡ ዘገባዎች አመልክተዋል። ቢያንስ አንድ ሰው እንደሞተ እና ከ200 በላይ ህንጻዎች እንደወደሙም ተዘግቧል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ@sputnik_ethiopia መተግበሪያ | X ላይ ይከተሉን
https://amh.sputniknews.africa
ጃፓን በሀገሪቱ የተከሰተውን የሰደድ እሳት ለማጥፋት ሠራዊቷን አሠማራች
ጃፓን በሀገሪቱ የተከሰተውን የሰደድ እሳት ለማጥፋት ሠራዊቷን አሠማራች
Sputnik አፍሪካ
ጃፓን በሀገሪቱ የተከሰተውን የሰደድ እሳት ለማጥፋት ሠራዊቷን አሠማራችየጃፓን የምድር ኃይሎች በምዕራባዊ ግዛቶች በኦካያማ እና ኢሂሜ የእሳት አደጋ መከላከል ሥራዎችን እንደተቀላቀሉ የጃፓን ዋና የካቢኔ ፀሐፊ ዮሺማሳ ሃያሺ ተናግረዋል። ሰደድ እሳቱ እሁድ... 24.03.2025, Sputnik አፍሪካ
2025-03-24T17:25+0300
2025-03-24T17:25+0300
2025-03-24T17:44+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2025
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий