"ኢትዮጵያ ሁልጊዜም ከፓን አፍሪካኒዝም ፊት ነች" ሲሉ የኢትዮጵያ መንግሥት ባለስልጣን ተናገሩ

ሰብስክራይብ
"ኢትዮጵያ ሁልጊዜም ከፓን አፍሪካኒዝም ፊት ነች" ሲሉ የኢትዮጵያ መንግሥት ባለስልጣን ተናገሩ የኢትዮጵያ የፓን አፍሪካኒዝም ተሟጋችነት በመላው ዓለም ያሉ ጥቁር ሰዎች ለመብታቸው እና ለሉዓላዊነታቸው እንዲታገሉ ባነሳሳው የዓድዋ ድል ለመጀመሪያ ግዜ እንደተንጸባረቀ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ የውጭ ፖሊሲ በጎረቤት ሀገራት እና በቀጣናዊ ውህደት ላይ ያተኮረ እንደሆነም አስረድተዋል። ኢትዮጵያ በተለያዩ መንገዶች በተለይም በመሠረተ ልማት ግንባታ እና በኤሌክትሪክ ኃይል መጋራት ቀጣናዊ ውህደትን እውን ለማድግ በንቃት እየሠራች ነው ሲሉም ተናግረዋል። ባለስልጣኑ በመካሄድ ላይ የሚገኘው የምስራቅ አፍሪካ የባህል እና ሥነ-ጥበብ ፌስቲቫል እና ተመሳሳይ ዝግጅቶች ለቀጣናዊ ውህደት፣ ለሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት መጠናከር እና ለኢትዮጵያ ፐብሊክ ዲፕሎማሲ መጎልበት ወሳኝ ናቸው ብለዋል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ@sputnik_ethiopia መተግበሪያ | X ላይ ይከተሉን
አዳዲስ ዜናዎች
0