ኢትዮጵያ እና ዚምባብዌ የሁለትዮሽ ኢኮኖሚያዊ ትብብራቸውን ለማጠናከር ተስማሙ

ሰብስክራይብ
 ኢትዮጵያ እና ዚምባብዌ የሁለትዮሽ ኢኮኖሚያዊ ትብብራቸውን ለማጠናከር ተስማሙ የኢትዮጵያ የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ከዚምባብዌ አቻቸው ምቱሊ ኑቹቤ ጋር በሁለቱ ሀገራት የጋራ ፍላጎቶች እና ትብብር ዙሪያ በዛሬው እለት ተወያይተዋል። በውይይቱ ሁለቱ ባለስልጣናት በቁልፍ ፖሊሲዎች እና ማሻሻያዎች ላይ ሃሳብ እንደተለዋወጡ እና ዚምባቡዌ ከኢትዮጵያ ውጤታማ የኢኮኖሚ ስትራቴጂ ለመማር ፍላጎት እንዳላት የገለጸችበት እንደነበር ገንዘብ ሚኒስቴር ያጋራው መረጃ ያሳያል።ሚኒስትር አህመድ ሽዴ የዚምባብዌን ፍላጎት በደስታ ተቀብለው ኢትዮጵያ መልካም ተሞክሮዎችን ለመለዋወጥ እና የሁለትዮሽ ትብብሯን ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል። @sputnik_ethiopia መተግበሪያ | X ላይ ይከተሉን
አዳዲስ ዜናዎች
0