በሶማሊያ የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ኃይል የረመዳን ፆምን አስመልክቶ ለአቅመ ደካሞች ድጋፍ አደረገወታደሮቹ በጌዶ ክልል ባርድሂር ከተማ ለሚገኙ ለችግር የተጋለጡ የሕብረተሰብ ክፍሎች ስኳር፣ ፓስታ፣ ዱቄት፣ ዘይት እና ቴምር የመሳሰሉትን የምግብ አቅርቦቶች እንደለገሱ ተነግሯል።የሻለቃው ኮማንደር ኮሌነል ሞላ ሹመት ወታደሮቹ ለደህንነት እና ሰብዓዊ ድጋፍ ቁርጠኛ ናቸው ማለታቸውን የአፍሪካ ሕብረት የድጋፍ እና የማረጋጋት ተልዕኮ በማህበራዊ ትሥሥር ገፁ አስታውቋል። የባርድሂር ወረዳ ኮሚሽነር ኢስማኢል ሼክ አብዲ "ሰላምን ከማረጋገጥ በተጨማሪ ለሕብረተሰቡ የምታደርጉትን ሰብዓዊ ድጋፍ አሳይታችኋል። ላደረጋችሁት ወቅታዊ ድጋፍ በጣም እናመሰግናለን" ብለዋል።የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ልዑክ ከዚህ ቀደም ለአካባቢው ሆስፒታል የመድኃኒት እና የህክምና ቁሳቁስ እገዛ ማድረጉ ይታወሳል።@sputnik_ethiopia መተግበሪያ | X ላይ ይከተሉን
https://amh.sputniknews.africa
በሶማሊያ የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ኃይል የረመዳን ፆምን አስመልክቶ ለአቅመ ደካሞች ድጋፍ አደረገ
በሶማሊያ የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ኃይል የረመዳን ፆምን አስመልክቶ ለአቅመ ደካሞች ድጋፍ አደረገ
Sputnik አፍሪካ
በሶማሊያ የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ኃይል የረመዳን ፆምን አስመልክቶ ለአቅመ ደካሞች ድጋፍ አደረገወታደሮቹ በጌዶ ክልል ባርድሂር ከተማ ለሚገኙ ለችግር የተጋለጡ የሕብረተሰብ ክፍሎች ስኳር፣ ፓስታ፣ ዱቄት፣ ዘይት እና ቴምር የመሳሰሉትን የምግብ... 19.03.2025, Sputnik አፍሪካ
2025-03-19T17:14+0300
2025-03-19T17:14+0300
2025-03-19T17:44+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2025
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий
በሶማሊያ የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ኃይል የረመዳን ፆምን አስመልክቶ ለአቅመ ደካሞች ድጋፍ አደረገ
17:14 19.03.2025 (የተሻሻለ: 17:44 19.03.2025)
ሰብስክራይብ