ሶስተኛው የአፍሪካ የማዕድን ፎረም በአዲስ አበባ መካሄድ ጀመረ

ሰብስክራይብ
ሶስተኛው የአፍሪካ የማዕድን ፎረም በአዲስ አበባ መካሄድ ጀመረ “የአፍሪካ የማዕድን ራዕይ ስኬቶች፣ ፈተናዎች እና እድሎች” በሚል መሪ ቃል የሚካሄደውን ፎረም፤ የአፍሪካ ማዕድናት ልማት ማዕከል እንዳዘጋጀው ተገልጿል፡፡ፎረሙ በማዕድን አስተዳደር፣ እሴት መጨመር እና ዘላቂነት ላይ የሚታዩ መዋቅራዊ እክሎችን መፍታት እና እድሎችን መጠቀም በሚቻልበት መንገድ ላይ ይመክራል ተብሏል። በማዕድን መስክ ያሉ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ የትኩረት መስኮችን ከአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና እና አጀንዳ 2063 ጋር ማጣጣም የፎረሙ ሌላ አጀንዳ ነው።     ፎረሙ እስከ መጋቢት 12 ድረስ የሚቆይ ሲሆን የአፍሪካ ሕብረት አባል ሀገራት እና ባለድርሻ አካላት በምክክሩ ላይ ይሳተፋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል።                                           @sputnik_ethiopia መተግበሪያ | X ላይ ይከተሉን
አዳዲስ ዜናዎች
0