ቬንዙዌላ ስደተኛ ዜጎቿን ለመቀበል ፈቃደኛ የማትሆን ከሆነ አሜሪካ አዲስ ማዕቀብ እንደምትጥል አስጠነቀቀች

ሰብስክራይብ
ቬንዙዌላ ስደተኛ ዜጎቿን ለመቀበል ፈቃደኛ የማትሆን ከሆነ አሜሪካ አዲስ ማዕቀብ እንደምትጥል አስጠነቀቀች "ቬኔዙዌላ ተመላሽ ዜጎቿን ከአሜሪካ የመቀበል ግዴታ አለባት። ይህ ለክርክርም ሆነ ለድርድር የሚቀርብ ጉዳይ አይደለም። ሽልማትም አያስገኝም። የማዱሮ አገዛዝ ያለ ተጨማሪ ሰበብ እና መዘግየት ተከታታይ የስደተኞች በረራዎችን የማይቀበል ከሆነ ዩናይትድ ስቴትስ አዲስ፣ ከባድ እና እየጨመረ የሚሄድ ማዕቀብ ትጥላለች" ሲሉ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ተናግረዋል። የሩቢዮ መግለጫ ዩናይትድ ስቴትስ ከ250 በላይ የቬንዙዌላ ትሬን ደ አራጓ የወንጀል ቡድን አባላትን ወደ ኤል ሳልቫዶር መላኳን ተከትሎ፤ በዋሽንግተን እና ካራካስ መካከል ያለው ግንኙነት እየሻከረ በመጣበት ወቅት የመጣ ነው። የአሜሪካን ድርጊት የተቹት የቬንዙዌላ ባለስልጣናት፤ ወንጀለኞቹን ለመቀበል ፈቃደኛ እንዳልሆኑ ገልጸዋል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ@sputnik_ethiopia መተግበሪያ | X ላይ ይከተሉን
አዳዲስ ዜናዎች
0