የኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግሥት እና የኤም 23 አማፂያን በአንጎላ ሊደራደሩ ነው

ሰብስክራይብ
የኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግሥት እና የኤም 23 አማፂያን በአንጎላ ሊደራደሩ ነው ቀደም ሲል ከኤም 23 ጋር ፊት ለፊት አልወያይም ይሉ የነበሩት ፕሬዝዳንት ፌሊክስ ሺሴኬዲ፤ አሁን ሀሳባቸውን በመቀየር ማክሰኞ በሉዋንዳ ድርድር ለማድረግ መወሰናቸው ትልቅ ለውጥ ነው ሲሉ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። የኤም 23 ቃል አቀባይ ላውረንስ ካንዩካ ቡድኑ በድርድሩ ላይ እንዲሳተፍ ከአንጎላ ጥሪ እንደቀረበለት እሁድ እለት በኤክስ ገፃቸው በኩል አሳውቀዋል። ቃል አቀባዩ ኤም 23 በድርድሩ ላይ የሚሳተፉ አምስት ልዑካኑን እንደሚልክ ሰኞ እለት አረጋግጠዋል። አደራዳሪዋ አንጎላ ለውይይቱ የበለጠ ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር አፋጣኝ የተኩስ አቁም እንዲደረግ ጠይቃለች። እነዚህ ሙከራዎች ቢደረጉም በዋሊካሌ ክልል በሳምንቱ መጨረሻ ላይ ግጭቶች እንደቀጠሉ ዘገባዎች ጠቁመዋል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ@sputnik_ethiopia መተግበሪያ | X ላይ ይከተሉን
አዳዲስ ዜናዎች
0