የጤና ሚኒስቴር የሀገር ውስጥ የፋርማሲዩቲካል አምራች ኢንዱስትሪዎች ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ ለመሆን መሥራት እንደሚገባቸው አሳሰበ

ሰብስክራይብ
የጤና ሚኒስቴር የሀገር ውስጥ የፋርማሲዩቲካል አምራች ኢንዱስትሪዎች ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ ለመሆን መሥራት እንደሚገባቸው አሳሰበበጤና ሚኒስትር ዴኤታ ፍሬሕይወት አበበ የተመራ ቡድን በኢትዮጵያ የፋርማሲዩቲካል አምራች ኢንዱስትሪዎች አንዱ የሆነውን ሂውማንዌል ፋርማሲዩቲካል ኢትዮጵያን ጎብኝቷል። በጉብኝቱ የሀገር ውስጥ የፋርማሲዩቲካል አምራች ኢንዱስትሪዎች በአቅርቦት ያላቸው ድርሻ እየጨመረ መሆኑን የጤና ሚኒስትር ዴኤታዋ ፍሬሕይወት አበበ ጠቁመዋል። ይህም የመድኃኒትና የሕክምና መገልገያ አቅርቦት እንዲኖር ለማስቻል ወሳኝ እንደሆነ የገለጹት ባለስልጣኗ፤ ምርቶቹ በሀገር ውስጥ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ በጥራት ተወዳዳሪ ሊሆኑ እንደሚገባ አሳስበዋል። በዚህ ረገድ ጤና ሚኒስቴር አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑንና ለዚህም ስኬት የሀገር ውስጥ የፋርማሲዩቲካል አምራች ኢንዱስትሪ ልማት ፎረም በማቋቋም ወደ ሥራ እንደተገባም ተገልጿል። መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦   APK ፋይል ሊንክ  ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0