ቅድሚያ ለሴቶች የ5 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር በአዲስ አበባ ተካሄደ በታላቁ ሩጫ ኢትዮጵያ እና አጋሮቹ ትብበር በተዘጋጀው ውድድር ላይ ከ16 ሺህ በላይ ሴቶች ተሳትፈዋል። ውድድሩ ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን በማስመልከት ''ሁሉም መብቶች ለመላው ሴቶች" በሚል መሪ ቃል ተካሄዷል። በኦሊምፒክ የድርብ ሜዳሊያ አሸናፊና የውድድሩ አምባሳደር አትሌት መሰረት ደፋር ከስፑትኒክ አፍሪካ ጋር ባደረገችው ቃለ ምልልስ፤ "ቅድሚያ ለሴቶች ውድድር ተምሳሌት የሆኑ ሴቶችን በማምጣትና ውድድሩ ላይ እንዲገኙ በማድረግ ትልቅ አስተዋፅኦ እያደረገ ነው። በተለይም ለአትሌቶች መውጫ ስለሆነ ትልቅና ለሴቶች አስተዋጽኦ ያለው ውድድር ነው" ስትል ተናግራለች። ውድድሩ እየሠራ ያለውን የግንዛቤ ለውጥ ለማስፋት በቀጣይ ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራትም ጭምር ተወዳዳሪዎች እንዲሳተፉ ሥራዎች ይሠራሉ ብላለች። መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
https://amh.sputniknews.africa
ቅድሚያ ለሴቶች የ5 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር በአዲስ አበባ ተካሄደ
ቅድሚያ ለሴቶች የ5 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር በአዲስ አበባ ተካሄደ
Sputnik አፍሪካ
ቅድሚያ ለሴቶች የ5 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር በአዲስ አበባ ተካሄደ በታላቁ ሩጫ ኢትዮጵያ እና አጋሮቹ ትብበር በተዘጋጀው ውድድር ላይ ከ16 ሺህ በላይ ሴቶች ተሳትፈዋል። ውድድሩ ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን በማስመልከት ''ሁሉም መብቶች ለመላው... 16.03.2025, Sputnik አፍሪካ
2025-03-16T14:03+0300
2025-03-16T14:03+0300
2025-03-16T14:44+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2025
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий