አሜሪካ ክርስቲያኖች ናይጄሪያ ውስጥ መሳደድ እየደረሰባቸው ነው ስትል ያቀረበችውን ክስ አቡጃ ውድቅ አደረገች ምላሹ የተሰጠው የሪፐብሊካን ኮንግረስ አባል ክሪስ ስሚዝ ናይጄሪያ ውስጥ በክርስቲያኖች ላይ የሚደርሰውን ጥቃት በማንሳት ሀገሪቱ በተለየ አሳሳቢ ሀገር ተብላ እንድትሰየም ሀሳብ ካቀረቡ በኋላ ነው። ስያሜው በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሚጸደቅ ከሆነ ናይጄሪያ ላይ ማዕቀብ ሊጣል ይችላል። ናይጄሪያ በ2020 በዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ወቅት ስያሜው ተሰጥቷት የነበረ ሲሆን፤ በ2021 በፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ከዝርዝሩ ወጥታለች። የናይጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አርብ እለት በሰጠው መግለጫ በሀገሪቱ ያለው ግጭት እና አለመረጋጋት ከሐይማኖት አድልዎ ጋር የተገናኘ አይደለም ብሏል። "በአብዛኛው ሙስሊሞች በሚገኙበት ሰሜን ናይጄሪያ ክፍል የሚታየው አመጽ እና ውንብድና በተለየ የትኛውም እምነት ወይም ሐይማኖት ተከታይ ላይ የተነጣጠረ አይደለም" ሲል ሚኒስቴሩ ገልጿል። በተጨማሪም ከቅርብ ግዜያት ወዲህ በናይጄሪያ ክርስቲያኖች እየተለዩ ይገደላሉ የሚሉ “የተሳሳቱ እና አሳች መረጃዎች መስፋፋታቸው” እንዳሳሰበው አስታውቋል። በአፍሪካ በሕዝብ ብዛት ቀዳሚ የሆነችው ናይጄሪያ በአብዛኛው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሚኖሩበት ደቡብ እና ሙስሊሞች በሚበዙበት ሰሜን መካከል እኩል ተከፍላለች። በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
https://amh.sputniknews.africa
አሜሪካ ክርስቲያኖች ናይጄሪያ ውስጥ መሳደድ እየደረሰባቸው ነው ስትል ያቀረበችውን ክስ አቡጃ ውድቅ አደረገች
አሜሪካ ክርስቲያኖች ናይጄሪያ ውስጥ መሳደድ እየደረሰባቸው ነው ስትል ያቀረበችውን ክስ አቡጃ ውድቅ አደረገች
Sputnik አፍሪካ
አሜሪካ ክርስቲያኖች ናይጄሪያ ውስጥ መሳደድ እየደረሰባቸው ነው ስትል ያቀረበችውን ክስ አቡጃ ውድቅ አደረገች ምላሹ የተሰጠው የሪፐብሊካን ኮንግረስ አባል ክሪስ ስሚዝ ናይጄሪያ ውስጥ በክርስቲያኖች ላይ የሚደርሰውን ጥቃት በማንሳት ሀገሪቱ በተለየ አሳሳቢ... 16.03.2025, Sputnik አፍሪካ
2025-03-16T13:10+0300
2025-03-16T13:10+0300
2025-03-16T13:44+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2025
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий
አሜሪካ ክርስቲያኖች ናይጄሪያ ውስጥ መሳደድ እየደረሰባቸው ነው ስትል ያቀረበችውን ክስ አቡጃ ውድቅ አደረገች
13:10 16.03.2025 (የተሻሻለ: 13:44 16.03.2025)
ሰብስክራይብ