የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚተሪ ፔስኮቭ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ያነሷቸው ነጥቦች፡-

ሰብስክራይብ
የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚተሪ ፔስኮቭ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ያነሷቸው ነጥቦች፡- ሩሲያ ዩክሬንን በተመለከተ ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሜሪካ አግኝታለች፡፡ ፑቲን በዩክሬን የሰላም ስምምነት ዙርያ የትራምፕን አቋም ቢደግፉም በጋራ ምላሽ የሚፈልጉ ጥያቄዎችን አንስተዋል፡፡ ሩሲያ እና አሜሪካ የፑቲን እና ትራምፕ ውይይት አስፈላጊ መሆኑን ተገንዝበዋል፡፡ ትራምፕ እና ፑቲን የሚገናኙበትን ትክክለኛ ቀን በተመለከተ መግባባት ላይ አልተደረሰም፡፡ ሩሲያ ገበያዋን ክፍት በማድረግ ለውጭ ኢንቨስተሮች ተዘጋጅታለች፡፡ ሩሲያ የውጭ ባለሀብቶች ጥለው በሄዱት ገበያ ውስጥ የሩሲያ ነጋዴዎችን አደጋ ላይ የሚጥል ምንም ነገር አትፈቅድም። ፑቲን የሞስኮ እና የካራካስ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረበትን 80ኛ ዓመት በማስመልከት ከቬንዙዌላ ፕሬዝዳንት ኒኮላስ ማዱሮ ጋር በዛሬው እለት በቪዲዮ ኮንፈረንስ ይገናኛሉ፡፡ ፑቲን በዛሬው እለት ከሩሲያ የጸጥታው ምክር ቤት ቋሚ አባላት ጋር ለመገናኘት እንዲሁም ዓለም አቀፍ የስልክ ጥሪ ለማድረግ ፕሮግራም ይዘዋል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦   APK ፋይል ሊንክ  ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0