በትግራይ ክልል ለተፈጠረው አለመረጋጋት መንስኤው አፈንጋጭ የህወሓት አንጃ እንደሆነ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ

ሰብስክራይብ
በትግራይ ክልል ለተፈጠረው አለመረጋጋት መንስኤው አፈንጋጭ የህወሓት አንጃ እንደሆነ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ በትግራይ ክልል ወቅታዊ ሁኔታ ዙርያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጌዲዮን ጢሞቴዎስ እና የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር ጌታቸው ረዳ በዛሬው እለት ለዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ ማብራሪያ ሰጥተዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጌዲዮን ጢሞቴዎስ ራሱን ነጥሎ የወጣው የህወሓት አንጃ የፕሪቶሪያው ስምምነት ሙሉ ለሙሉ እንዳይተገበር እንቅፋት መሆኑን በመድረኩ ገልጸዋል። የፌደራል መንግሥት የፕሪቶሪያው ስምምነት ሙሉ ለሙሉ እንዲተገበር እየሠራ እንደሆነና የክልሉን ወቅታዊ ሁኔታ በጥሞና በመከታተል ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታቸው ረዳ በበኩላቸው፤ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ እና የፌደራል መንግሥት በክልሉ ዘላቂ ሰላም ግንባታ ያላቸውን ሚና አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል። መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦   APK ፋይል ሊንክ  ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0