የአፍሪካ ሕብረት የትግራይ ክልል ጉዳይ እንዳሳሰበው ገለጸ

ሰብስክራይብ
የአፍሪካ ሕብረት የትግራይ ክልል ጉዳይ እንዳሳሰበው ገለጸሕብረቱ ዛሬ ባወጣው መግለጫ በትግራይ ያለውን ሁኔታ እየተከታተለ እንደሆነ በመግለጽ የክልሉ ሰላም እና መረጋጋት ወሳኝ እንደሆነ አስረግጧል፡፡ ሁሉም አካላት ከግጭት በመቆጠብ ውይይት እንዲያደርጉ እና ጥቅምት 23 ቀን 2015 ዓ.ም በተደረሰው የፕሪቶሪያ ስምምነት መሠረት  እንዲገዙ ሕብረቱ አሳስቧል።ለፕሪቶሪያ ስምምነት መገዛት የተገኘውን ሰላም ለመጠበቅ እና ለዘላቂ የሰላም ግንባታ፣ እርቅ እና ልማትን የሚደግፍ ሁኔታ ለመፍጠር ወሳኝ መሆኑንም ገልጿል። የአፍሪካ ሕብረት ለፕሪቶሪያ ስምምነት ትግበራ የማይቋረጥ ድጋፍ እንደሚያደርግ በመግለጫው አስታውቋል፡፡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦   APK ፋይል ሊንክ  ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0